አዲስ መጽሐፍ ለአንባብያን!

ቀደም ሲል የድርሻዬን የተወጣሁ መስሎኝ ሦስት የሚኾኑ መንፈሳዊ ይዘት ያላቸው መጻሕፍትን አዘጋጅቼ ለአንባብያን ማበርከቴን የሚያውቁ ወዳጆቼ ሁሉ ባገኙኝ ቁጥር አንድ ጥያቄ አዘወትረው ይጠይቁኛል፡፡ ጥያቄውም “መጽሐፍ ማዘጋጀትን ስለምን ትጦማለህ?” የሚል ነው፡፡  መጦም ዐውቆ ወሥኖ መከልከል ሲኾን እኔ ግን እየጦምሁ ሳይኾን ረሀብተኛ ስለኾንሁ ነው የሚል ምላሽ ስሰጥ ቆይቻለሁ፡፡ የሚበላው አጥቶ ያለ ሰው ጦመ ሳይኾን ተራበ መባል አለበትና፡፡ ይሁን እንጂ የምበላውም የማበላውም ባይኖረኝ እምነቴን እንድገልጥ የሚያስገድድ አንድ ወሣኝ ጉዳይ ገጠመኝ፡፡ “ወልደ አብ” በሚል ስም ተቀብቶ (ተሸፍኖ) አንድየክሕደት መጽሐፍ ብቅ አለ፡፡ ከቦታ መርጦ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በር አጠገብ እንደ ልብ ሲቸበቸብ ዐየሁ፡፡ የእነ መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬን፣ የእነ አለቃ አያሌው ታምሩን ቤተ ክህነት ጊዜ ዐይተው ሲዳፈሩት ሳይ ዘልቆ ተሰማኝ፡፡

ጋኖች ሲያልቁ ምንቸቶች ጋን ይኾናሉ፡፡ ቁጭ ብሎ ጋኖቹ እስኪመጡ መጠበቅ ይሻላል ወይስ ባታጠረቃም በምንቸቷ የአቅሜን ውኃ ልቅዳ? የልቤ ክርክር ነበረ፡፡ በምንቸትነቴ የጋኖቹን ሥራ እንድሠራ ዘመኑ አስገደደኝ፡፡ ከአቅሜ በላይ እንደኾነ ባውቅም ጋኖቹ እስኪመጡ ብፈነዳም እንኳ የሌሉቱን የጋኖቹን ድርሻ በችሎታዬ መጠን እየሠራሁ ልጠብቅ ብዬ ወሠንሁ፡፡ ያለውን የሰጠ ከንፉግ አይቆጠርም የሚለው ጥንታዊ አባባል አተጋኝ፡፡

ስለዚህም አሁን ስሟ ጌራ መድኃኒት የኾነችውን መጽሐፍ ማዘጋጀት ጀመርሁ፡፡ ከፍጸሜ በደረሰችልኝ ጊዜም የጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ “ወልደ አብ” የተባለውን መጽሐፈ ኑፋቄ አወገዘው፡፡ ከመወገዙ አስቀድሞ እንደ ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ፣ መምህር ወልደ አብርሃም በመጽሐፍ አሳምረው ድራሹን አጥፍተው ጽፈዋል፡፡ መልካሙ በየነ የሚባል አንድ ወንድማችን እና በብርዕ ስሙ በአማን ነጸረ የሚባል ቀንዳም ተሟጋች የድርሻቸውን ሲያበረክቱ በሩቅ ዐይቻለሁ፡፡ ከእነዚህ ተራ ለመሰለፍ ሻትሁና ገባሁበት፡፡ አሁን ከ፬፻፶ (450) ገጾች በላይ ያላት መጽሐፍ ኾናለች፡፡

ማተሚያ ቤቱ ባፈጠነልኝ መጠን ቶሎ ለአንባብያን አደርሳታለሁ ብዬ ተፍ ተፍ እያልሁ እገኛለሁ፡፡ ፈቃደ እግዚአብሔር ቢኾን “ሰርግ” ቢጤ ሳልደግስላት አልቀርም፡፡ የሰርጓንም ቀን ጊዜው ሲደርስ ዐሳውቃለሁ፡፡ በጸሎታችሁ ተራዱኝ! Continue reading

“የመጽሐፍ ምርቃት በዓምደ ሃይማኖት!” ተካሔደ

ሙሐዘ ቅዱሳን (የቅዱሳን ምንጭ) በሚል ርዕስ በዘሪሁን መንግሥቱ የተዘጋጀ ሁለተኛው መጽሐፍ በመንበረ መንግሥት (ግቢ) ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት አዳራሽ ታኅሣሥ 15 ቀን 2010 ዓ.ም. ተመረቀ፡፡

መርሐ ግብሩ በጸሎት ከተጀመረ በኋላ የታኅሣሥ ቅዱስ ገብርኤልን እና የጥምቀት በዓል ለማክበር ከእስራኤል የመጣችው ዘማሪት ማክዳ ቀለመወርቅ የመክፈቻ መዝሙር  አቅርባለች፡፡

መርሐ ግብሩ በጸሎት ከተጀመረ በኋላ የታኅሣሥ ቅዱስ ገብርኤልን እና የጥምቀት በዓል ለማክበር ከእስራኤል የመጣችው ዘማሪት ማክዳ ቀለመወርቅ የመክፈቻ መዝሙር  አቅርባለች፡፡

የመጽሐፉን ርዕስ ሙሐዘ ቅዱሳን (የቅዱሳን ምንጭ) ብሎ እንደሰየመው አዘጋጁ ሲያብራራ የፍጥረታት ፈጣሪ፤ የሁሉ ነገር አስገኚ የኾነው እግዚአብሔር በሥራ ለመሰሉት ቅዱሳን “እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ቅዱስ ነኝና እናንተም ቅዱሳን ኹኑ” በማለት አስተምሯል /ዘሌ. 19፥21/፡፡ እግዚአብሔር ቅዱስ፣ ፍጹም እንደሆነ ሁሉ እርሱ ያከበራቸው በረድኤት ያደረባቸው፣ በጸጋ የተዋሐዳቸው የሃይማኖት ሰዎች ቅዱሳን ይባላሉ፡፡ ይህንን አምላካዊ ትእዛዝ ሰምተው በተግባር የተረጐሙ፣ ፈጣሪያቸውን ያስደሰቱ፤ ፈጣሪያቸው ያከበራቸውና ያስከበራቸው ሰዎች እንዳሉ ቅዱሳት መጻሕፍት ምስክር ናቸው፡፡ ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ በመልእክቱ “ዳሩ ግን እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ኹኑ ተብሎ ስለተጻፈ የጠራችሁ ቅዱስ እንደኾነ፤ እናንተም ደግሞ በኑሮአችሁ ቅዱሳን ኹኑ” በማለት የጸጋ ቅድስና ለቅዱሳን የተሰጠ መኾኑን ያረጋግጥልናል /1ኛ ጴጥ.1፥15/፡፡

ቅዱሳን በሃይማኖት በምግባር እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኙ፣ በንጽሕና በቅድስና ያጌጡ በገድል የተመላ ሕይወት አላቸው፡፡ ለዚህም ነው የነገረ መለኮት ምሁራን /Theologian/ “ያለ ነገረ ቅዱሳን ነገረ እግዚአብሔርን መናገር፣ ያለ ቅዱሳንም እግዚአብሔርን በትክክል ማወቅ አይቻልም” የሚሉት፤ ምክንያቱም ቅዱሳን የእግዚአብሔር መገለጫዎች በመኾናቸው፤ እነርሱን በመመልከት ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ መናገርና መመስከር ይቻላል፡፡ በአጠቃላይ ነገረ ቅዱሳን የነገረ እግዚአብሔር ትምህርት አንዱ ክፍል ነው፡፡

ቅዱሳን ሀብታቸው ጸጋቸው ከእግዚአብሔር የተገኘ ነው፡፡ ትንቢት ቢናገሩ፣ ድውይ ቢፈውሱ፣ ሙታን ቢያስነሡ ከእግዚአብሔር የተቀበሉትና በስሙ የሚፈጽሙት አገልግሎት ነው፡፡ የቅዱሳን ሥልጣን ምድራዊ ብቻ ሳይኾን ሰማያዊም ነው፡፡ ቅዱሳን በምድር ብቻ ሳይሆን በሰማይም ያለ ማቋረጥ ይለምኑልናል፤ ይጸልዩልናል፣ ያማልዱናል “የጻድቃን ማደሪያቸውን የቅዱሳንን ቦታቸውን አየኹ፡፡ ከዚያም ቦታ ዐይኖቼ ከመላእክት ጋር የሚኖሩበት ማደሪያቸውን ከቅዱሳንም ጋራ የሚኖሩበት ቦታቸውን አዩ፡፡ ስለ ሰውም ልጆች ፈጽመው ይለምናሉ፣ ይጸልያሉ” /ሄኖ.7፣60/፡፡

ሙሐዘ ቅዱሳን የቅዱሳን ምንጭ ማለት ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስን በፍጹም ሕይወታቸው ለሚመስሉት ቅዱሳን ቅድስናን በተግባር ሠርቶ ሥሩ ያለ፤ ቅዱሳንን የጠራ፣ የተቀበለና ያከበረ እውነተኛው የቅዱሳን ምንጭ /አስገኚ/ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያንም የክርስቶስ አካል በመኾኗ፤ የቅዱሳን ምንጭ ናት፡፡ በመኾኑም ቤተ ክርስቲያንን ከቅዱሳን፤ ቅዱሳንንም ከቤተክርስቲያን መነጠል አይቻልም፡፡  ቤተ ክርስቲያን በተለያዩ ዘመናት በዓላውያን ነገሥታት፣ በመናፍቃን ብትፈተንም ሙሐዘ ቅዱሳን (የቅዱሳን ምንጭ) ናትና ዐውሎ ነፋሱ፣ ወጀቡ ሳያጠፋት የቆየችው ባፈራቻቸው አያሌ ቅዱሳን ነው፡፡ ቅዱሳን ልጆቿ ወንጌል አስተምረው፣ በገድል ተቀጥቅጠው፣ ቤተ ክርስቲያንን ጠብቀው ለዚህ ትውልድ እንድትደርስ አድርገዋታል፡፡”

መጽሐፉ በውስጡ ስለያዛቸው ቁም ነገሮች ሲገልጽ “መጽሐፉ በሰባት ምዕራፍ የተዘጋጀ ሲሆን፤ በመጀመሪያው ምዕራፍ የቅድስና ምንነትና ትርጉም፣ ቅድስና የሚሰጠው ለማን ነው? ቅዱሳን የሚባሉት እንማን እንደሆኑ በመግለጽ ስለቅዱሳን ታሪክና ሥራዎቻቸውን ፍንትው አድርጎ ያሳያል፡፡ ሁለተኛው ምዕራፍ ለቅዱሳን የተሰጡ ጸጋዎች ምን ምን እንደኾኑ በስፋት ይዘረዝራል፡፡ በሦስተኛው ምዕራፍ እግዚአብሔር በሕይወተ ሥጋ ላገለገሉትና ላስደሰቱት ለቅዱሳን ባለሟሎቹ በዕለተ ሞታቸው ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል፡፡ ይህም ኪዳን ዘላለማዊ በመኾኑ የሚለምኑትን ይቅር ሲላቸውና ሲምራቸው ይኖራል፡፡

ምዕራፍ ዐራት የቅድስና ደረጃዎች (መዓርጋተ ቅዱሳን) ስለሚባሉት ቅዱሳን በተጋድሎ የሚያገኙአቸውን ዐሥሩን ደረጃዎች በዝርዝር ይተነትናል፡፡ ምዕራፍ አምስት የእግዚአብሔር ባለሟል የሆኑ ቅዱሳንን እንዴት ማክበር እንዳለብንና በማክበራችን የምናገኘውን ጥቅም ያስረዳናል፡፡ ምዕራፍ ስድስት የቅዱሳን ተጋድሎ የያዙትን መጻሕፍት ምንነትና የቅዱሳንን ሕይወት ታሪክና ሥራዎቻቸውን በየትኞቹ መጻሕፍት ላይ እንደምናገኝ መረጃ ይሰጠናል፡፡ እነዚህን መጻሕፍት  ብናነብ የምናገኛቸውን ጥቅም በስፋት ያትታል፡፡ በመጨረሻም በምዕራፍ ሰባት ከቅዱሳን ተጋድሎ በመማር የራሳችንን የሕይወት ጎዳና እንዴት መምራት እንዳለብን የሚመክሩ ርእሰ ጉዳዮችን የያዘ ነው፡፡” በማለት መጽሐፉን ያዘጋጀበትን ምክንያት አጠቃሏል፡፡

 የአዘጋጁን ገለጻ እንዳበቃ የዓምደ ሃይማኖትሰንበት ት/ቤት መዘምራን ያሬደዊ መዝሙር አቅርበዋል፡፡

መጽሐፉ ሲዘጋጅ ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ የአርትኦት ሥራውን የተወጡት ቀሲስ ሰሎሞን ወንድሙ መጽሐፉ ስላለው ጠቀሜታ የሚከተለውን አስተያየት ሰጥተዋል፡፡

“ቅድስና የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ በመኾኑ ዘወትር ቅዱስ እምቅዱሳን፣ ልዑል እምልዑላን፣ አምላከ አማልክት፣ እግዚአ አጋእዝት ወንጉሠ ነገሥት በማለት እንጠራዋለን፡፡ የልዑል እግዚአብሔር ቅድስና በባሕርዩ የነበረና የሚኖር፣ ከፍጡራን የተለየ፣ ተነጻጻሪ የሌለውና በቃላት ይኽንን ይመስላል የማይሉት ፍጹም ነው፡፡

በኦሪት ዘሌዋውያን ምዕራፍ ፲፩ ቁጥር ፵፭ ላይ እኔ ቅዱስ ነኝና እናንተ ቅዱሳን ኹኑ፡፡ በማለት እንደተናገረው አስቀድሞ ከእናታቸው ማኅጸን የመረጣቸውን፣ ለአገልግሎት የጠራቸውን፣ ያጸደቃቸውንና ያከበራቸውን ቅዱሳን በማለት እንጠራቸዋለን፡፡

Continue reading

አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ

በመ/ር ተስፋሁን ነጋሽ የተዘጋጀው ወደ ሮሜ ሰዎች መጽሐፍ ታትሞ በገበያ ላይ ውሏል፡፡ መጽሐፍ በቤተ ክርስቲያናችን ሊቃውንት ታርሞና ተስተካክሎ የቀረበ ሲሆን፤ ለመምህራን፣ ለደቀ መዛሙርት፣ ለሰንበት ት/ቤት ተማሪዎችና ለምእመናን ሁሉ ጠቀሜታው የጎላ ነው፡፡

ስለሆነም መጽሐፉን በማንበብ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተጋብዘዋል፡፡ መጽሐፉን መግዛት የምትፈልጉ በሁሉም መጻሕፍት መሸጫ ያገኙታል፡፡

ለጸሐፊው አስተያየት መስጠት ከፈለጋችሁ +251 919 339 523 መደወል ትችላላችሁ፡፡

ቤተክርስቲያንና ቅርሶችዋ

በክፍል አንድ ምልከታችን የቤተክርስቲያናችን ቅርሶች የሀገሪቱን ገቢ ከማሳደግ አኳያ ያደረጉትን ጠቀሜታ ተመልክተናል፡፡ ተከታዩን ክፍል እነሆ መልካም አዲስ ዓመት ይሁንላችሁ

የሀገር ገጽታ ይገነባሉ፤ አንድነትንም ያጠነክራሉ 

ቅርሶች የአንዲት ሀገር መለያ ምልክቶች ናቸው፡፡ሕዝቡ ስለ ሀገሩ የበለጠ እንዲያውቅና እንዲማር ከመርዳታቸውም በላይ ብሔራዊ ስሜትንና የሀገር ፍቅርን አንድነትን ያጠነክራሉ፡፡ ቅርሶች ብሔራዊና ዓለም አቀፋዊ ይዘት ስላላቸው የታሪክና የባሕል መረጃ በመሆናቸው የሀገርን ገጽታ በመገንባት ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ ያደርጋሉ፡፡ወደ ሀገሪቱ የቱሪስት ፍሰቱም እንዲጨምር ያደርጋሉ፡፡

images-1

ለምጣኔ ሀብታዊ / Economy/ጠቀሜታ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የማንነት መገለጫዎቿ የሆኑ በርካታ ቅርሶቿ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪው ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው፡፡ ለአንድ ሀገር እድገት ምጣኔ ሀብት ግንባት ጪስ አልባው ኢንዱስትሪ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል፡፡የቱሪስትን ልብ የሚያማልሉ ገዳማቷ፣ንዋያተ ቅድሳቷ፣ ፍልፍልን ውቅር አብያተ ክርስቲያናቷ፣ በርካታ ምዕተ ዓመታትን ያስቆጠሩ ቅዱሳት ሥዕላቷ፤ የዕውቀት ብርሃን እንደ ጠዋት ጮራ የሚፈነጥቅባቸው የአብነት ትምህርት ቤቶቿ፣ ዜማዋ፣ የብራና መጻሕፍቷ እስከ ዛሬ ይጎበኛሉ፡፡ እነዚህ የቱሪስት መስህብ የሆኑ ቅርሶቻ ሲጎበኙ የገቢ ምንጭ፣የሥራ ዕድል ይፈጥራሉ፡፡ የውጭ ምንዛሪ ያስገኛሉ፡፡

አገር አቋርጠው አዲስ ነገር ለማየት ጓግተው የመጡ ቱሪስቶች የዐይን ማረፊያ የሆነችው ቤተክርስቲያን ለሀገራችን የምጣኔ ሀብት ዕድገት የውጭ ምንዛሬን በማስገኘት ረገድ የምታበረክተው አስተዋጽኦ እጅግ የላቀ ነው፡፡

ሃይማኖታዊ ጠቀሜታ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅርሶች ከፍተኛ የሆነ ሃይማኖታዊ ጠቀሜታ አላቸው፡፡ ቅርሶች ለሃይማኖታችንና ለማንነታችን ካላቸው ማሳያነት ባሻገር አብዛኛዎቹ በቅብዐ ሜሮንና በቡራኬ የከበሩ በመሆናቸው የተለዩና የተቀደሱ ናቸው፡፡ በመሆኑም እነዚህን ቅርሶች ቀርቦ ማየት መንፈሳዊ እርካታ ያስገኛሉ፡፡ ለምሳሌ፡- መንፈሳዊ በዓላት በመሳተፍ፣ቅዱሳትን መካናትን በመሳለም፣ መንፈሳዊ ክንዋኔዎች( ቅዳሴ፣ በሰዓታት መሳተፍ…) መንፈሳዊ እርካታን ያስገኛሉ፡፡

images

ለአካባቢ ጥበቃ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጋሉ

ቤተክርስቲያን ከምትጠብቃቸውና ከምትንከባከባቸው ቅርሶች አጸዶች(ደኖችም) ከፍተኛውን ሥፍራ ይይዛሉ፡፡እነዚህ አጸዶች ሀገር በቀል የሆኑ በሌላ ቦታ የማይገኙ እንደሆኑ ጥናቶች ያሳያሉ፡፡በሀገራችን ረጅም ዘመናት ያስቆጠሩ ለአካባቢ አየር ከፍተኛ ጠቀሜታ ያላቸው ሀገር በቀል ደኖች የሚገኙት ቤተክርስቲያን ነው፡፡እነዚህ ደኖች ቅዱሳን የሚጸልዩባቸው፣ዐጽመ ቅዱሳን ያረፉባቸው ከመሆናቸውም በላይ በርካታ አዕዋፍ፣አራዊት የሚገኙባቸው የሕይወት መስተጋብር እንዳይጠፋ የሚያደርጉ ናቸው፡፡ ስለዚህ ቤተክርቲያን  በረሓማነትን ለመቀነስ፣አካባቢን ለመጠበቅ በደን ጥበቃ የምታበረክተው አስተዋጽኦ  ከፍተኛ ነው፡፡

በዓለም ቅርስነት የተመዘገቡ የቤተክርስቲያን ቅርሶች

ሀገራችን ኢትዮጵያ በረጅም ጊዜ ታሪኳ ያፈራቻቸው በርካታ ባሕላዊ ቅርሶች አሏት፡፡ ከእነዚህም መካከል ጥቂቶቹ ዓለም አቀፋዊ መስፈርቶችን አሟልተው በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባሕል ድርጅት /UNESCO/ በዓለም ቅርስነት ተመዝግበው ይገኛሉ፡፡

ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት ኤጀንሲ በተገኘው መረጃ መሠረት ሀገራችን ዐሥራ ሁለት የብራና መዛግብትን በዓለም ቅርስነት አስመዝግባለች፡፡ መዛግብቱም፡- አርባዕቱ ወንጌል፣ የጳውሎስ መልእክት፣ መዝሙረ ዳዊት፣ ግብረ ሕማማት፣ መጽሐፈ ሄኖክ፣ መጽሐፈ ቅዳሴ፣ የዳግማዊ ምኒልክ ታሪክ፣ነገሥት፣ታሪከ ነገሥት፣ ዐፄ ቴዎድሮስ ለእንግሊዝ ንግሥት ቪክቶሪያ የጻፉት ደብዳቤ፣የሸዋው ንጉሥ ሣህለ ሥላሴ ለእንግሊዝ ንግሥት የጻፉት ደብዳቤ ናቸው ስድስቱ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለሃይማኖታዊ አገልግሎት ይውሉ የነበሩ፣ሦስቱ ነገሥታቱ ለውጭ መንግሥታት የላካቸው ደብዳቤዎች እና ሦስቱ ደግሞ የታሪክ እና አስተዳደር ቀመስ መጻሕፍት ናቸው /ከኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት ኤጀንሲ ተገኘ መረጃ/፡፡

ከላይ ከተገለጹት መዛግብት በተጨማሪ ሌሎች ሦስት ጥንታዊ የብራና መጻሕፍት በዓለም ቅርስነት ለመመዝገብ በእጩነት ቀርበዋል፡፡ መጻሕፍቱም፡- መጽሐፈ ጤፉት፣ ርቱዐ ሃይማኖት እናመጽሐፍ ቅዱስ ናቸው

images-212

ቤተክርስቲያን በቅርሶቿ ተጠቃሚ ናት?

በኢትዮጵያ ከሚገኙት በርካታ ታሪካዊ ቅርሶችዋ በአብዛኛው የቤተክርስቲያን ሀብቶች  በመሆናቸው፤ቤተክርስቲያኗ ለእነዚህ ቅርሶች ሕጋዊ ባለቤት ናት፡፡ ቤተ ክርስቲያን ከቅርሶቿ የምታገኘውን ገቢ የመጠቀም ሕጋዊ መብት አላት፡፡ ይሁን እንጂ ከቅርሶቿ ሙሉ በሙሉ ተጠቃሚ ናት ብሎ ለማለት እንደማያስደፍር በዘርፉ ጥናት ያደረጉ ምሁራን ያስረዳሉ፡፡ Continue reading

ቤተክርስቲያንና ቅርሶችዋ

ሀገራችን ኢትዮጵያ የበርካታ ሃይማኖታዊ እና ባሕላዊ የቅርሶች ባለቤት ናት፡፡ በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስ እና ባሕል ድርጅት /UNESCO/ ከተመዘገቡት የሀገሪቱ ቅርሶች ውስጥ በአብዛኛው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ይዞታ ሥር የሚገኙ ናቸው፡፡ በቤተክርስቲያናችን ውስጥ ከሚገኙት ቅርሶች ዐሥራ ሁለት የሥነ ጽሑፍ ሀብቶቻችን በዓለም ቅርስነት እንደተመዘገቡ ጥናቶች ያሳያሉ /የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ጥናት መጽሔት፣ቁጥር 1፤2002 ዓ.ም፡፡

ቅርስ ምንድን ነው?

የቅርስን ትርጉም የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን መሥሪያ ቤት  በየጊዜው ጽንሰ ሐሳቡና የሚያካትታቸው ነገሮች እየሰፉና እየበዙ የመጡ መሆናቸውን በተለያየ ጊዜ በሀገሪቱ የቅርስ አጠባበቅን በተመለከተ ከተደነገጉት ሕጎች መረዳት ይቻላል፡፡የመጀመሪያው በነጋሪት ጋዜጣ የወጣው የጥንታዊ ታሪካዊ ቅርሶች አስተዳደር ዐዋጅ ቁጥር 229/1958 ቅርስን ሲተረጉም፡- “ጥንታዊ ቅርስ ማለት ከ1850 በፊት የተሠራ ማንኛውም ዓይነት ሰው ሠራሽ ሥራ ወይም ዕቃ ማለት ነው” በማለት ሲገልጽ፤ስለ ቅርስ ጥናትና አጠባበቅ የወጣው ዐዋጅ ቁጥር 209/1992 “ቅርስ” ማለት፡- “በቅድመ ታሪክና በታሪክ ዘመን የሰው ልጅ የፈጠራና የሥራ እንቅስቃሴ ውጤት የሆነ የተፈጥሮ የለውጥ ሂደትን የሚገልጽና የሚመሰክር በሳይንስ፣በታሪክ፣በባሕል፣በሥነ ጥብብና በዕደ ጥብብ ይዘቱ ከፍተኛ ተፈላጊነትና ዋጋ ያለው ማናቸውም ግዙፍነት ያለውና ግዙፍነት የሌለው ነገር ነው” ሲል ተርጉሞታል፡፡ /ነጋሪት ጋዜጣ፤1992ዓ.ም/፡፡

ከላይ ያየናቸው በአገራችን በተለያየ ጊዜ ስለ ቅርስ የተሰጡት የሕግ ትርÙሜዎች መጠነኛ ልዩነት ቢያሳዩም ዋናው የምንገነዘበው ቁም ነገር ከጊዜ ወደ ጊዜ የቅርስ ትርጉምና የሚያካትታቸው ነገሮች እየሰፉ መምጣታቸውን ነው፡፡በአጠቃላይ ቅርስ የሰው ልጅ በምድር ላይ መኖር ከጀመረበት ጊዜ አንሥቶ አሁን እስከደረሰበት ከፍተኛ የሳይንስና የቴክኖሎጂ ዘመን ድረስ የነበረውን ረጅም የሥልጣኔ የዕድገት ጉዞ የሚያሳይ የታሪክ፣የባሕልና የተፈጥሮ መረጃ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅርሶች ለሃይማኖታችንና ለማንነታችን ካላቸው ማሳያነት ባሻገር አብዛኛዎቹ በቅብዐ ሜሮንና በቡራኬ የከበሩ በመሆናቸው የተለዩና የተቀደሱ ናቸው፡፡

 images

 የቅርስ ዓይነቶች

 የተባበሩት መንግሥታት የትምህርትና የሳይንስ የባሕል ድርጅት /UNESCO/ ስለ ቅርስ የሰጠውን ትርÙሜና በሀገራችን በ1992 ዓ.ም በወጣው ዐዋጅ ላይ በተካተተው መሠረት ቅርስ በሁለት ይከፈላሉ፡፡ እነዚሀም፡-

  1. ግዙፍነት የሌለው ቅርስ /Intangble Cultural Heritage/

    ግዙፍነት የሌለው ቅርስ የሚባሉት ሥነ በዓላት ፣የሊቃውንቱ ሥነ አእምሮአዊ ዕውቀት ወዘተ ናቸው፡፡

  1. ግዙፍነት ያለው ቅርስ /Tangble Cultural Heritage/

      ግዙፍነት ያለው ቅርስ በእጅ የሚዳሰሱ፣በዐይን የሚታዩ የሚንቀሳቀሱና የማይንቀሳቀሱ ባሕላዊና ታሪካዊ ወይም ሰው ሠራሽ ቅርሶች ናቸው፡፡እነዚህ ግዙፍነት ያላቸው ቅርሶች /Tangble Cultural Heritage/ ከባሕርያቸው አንጻር በሁለት መልክ ይመደባሉ፡፡

  ሀ. የሚንቀሳቀሱ /Movable  Cultural Heritage/

      ግዙፍነት ያለው የሚንቀሳቀስ ቅርስ ማለት ከቋሚ ነገሮች ጋር በመሠረትነት ያልተገነቡና ከቦታ ቦታ በቀላሉ ሊንቀሳቀሱ የሚችሉ ናቸው፡፡እነዚህም፡-የብራናና የድንጋይ ላይ ጽሑፎች፣ ከወርቅ፣ከብር ፣ከነሐስና ከሌሎች የተሠሩ ገንዘቦች ወዘተ ናቸው፡፡

  ለ. የማይንቀሳቀሱ/Imovable Cultural Heritage/ 

ግዙፍነት ያለው የማይንቀሳቀስ ቅርስ ማለት በአሠራርም ሆነ በተፈጥሮ ከቦታ ወደ ቦታ ሊንቀሳቀሱ የማይችሉ በመሠረት ተገንብቶ ቋሚ ከሆነ ነገር ጋር የተያያዙ ናቸው፡፡እነዚህም፡- መካነ ቅርሶች የተገኙባቸው ቦታዎች፣ሐውልቶች፣አብያተ ክርስቲያናት ፣ገዳማት አድባራት ወዘተ ናቸው፡፡/ነጋሪት ጋዜጣ፤1992 ዓ.ም፡፡Mengistu Gobezie፤Yemirhane Kristos:A Bridge between Axum and Laibela Civilization;2011;pp…/፡፡ Continue reading

የነጽሮተ ሀገር መጽሐፍ ምረቃ ምን ይመስላል?

ነጽሮተ ሀገር በሚል ርዕስ በዘሪሁን መንግሥቱ የተዘጋጀ መጽሐፍ ፒያሳ በሚገኘው በመናገሻ አራዳ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊየርጊስ ቤተ ክርስቲያን ስብከተ ወንጌል አዳራሽ የካቲት 28 ቀን 2007 ዓ.ም. ተመረቀ፡፡

10999978_858644100862300_7766493882891550577_n

የዕለቱ መርሐ ግብር መሪ መ/ር ዳንኤል ሞገስ

የዕለቱ መርሐ ግብር መሪ
መ/ር ዳንኤል ሞገስ

‹‹ነጽሮተ ሀገር›› (ሀገርን ማየት) በሚል ርዕስ የመጽሐፉን መጠሪያ ለምን እንዳለው ሲያብራራ ስለ ኢትዮጵያ ጥንታዊነት፣ ስለ ቅርሶቿ፣ የቱሪስት መስህብ መሆኗንና የቤተ ክርስቲያንን ሐዋርያዊ ተልእኮ የሚዳስስ ስለሆነ፤ መጠሪያን ነጽሮተ ሀገር ብዬዋለሁ፤ በማለት ለታዳሚዎቹ አስረድቷል፡፡

አዘጋጁ መጽሐፉ ስለያዛቸው ቁምነገሮች ሲያብራራ

አዘጋጁ መጽሐፉ ስለያዛቸው ቁምነገሮች ሲያብራራ

መጽሐፉ በውስጡ ስለያዛቸው ቁም ነገሮች ሲገልጽ በአምስት ምዕራፎች ተከፍሎ የተዘጋጀ ሲሆን፤ በመጀመሪያው ምዕራፍ የኢትዮጵያ የስሟ ትርጓሜ፤ የሀገሪቷ መገለጫዎች ፍንትው አድርጎ ያሳያል፡፡ በሁለተኛው ምዕራፍ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለሀገሪቱ ያበረከተችው አስተዋጽኦ ምንድን ናቸው የትናንቱን በዛሬው መስታወትነት እንድንመለከት በማድረግ፤ የኢትዮጵያ ታሪክ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጋር ያለውን ቁርኝት ምን እንደሚመስል መረጃ ይሰጣል፡፡
በሦስተኛው ምዕራፍ የቤተክርስቲያኗን ዓለም አቀፍ ግንኙነት ከክርስትና በፊትና በኋላ ምን ይመስል እንደነበር ያሳያል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ባደረገችው ግንኙነት ያገኘችውን ጥቅምና ጉዳት ይፈትሻል፡፡ ይህን መነሻ በማድረግ በምዕራፍ አራት ኢትዮጵያ መንበረ ፕትርክና እንዴት እንዳገኘች፣ በዘመኑ የነበሩ ነገሥታት ያበረከቱትን አስተዋጽኦ፤ ከግብጽ ወደ ኢትዮጵያ ተሹመው የመጡ ጳጳሳት አገልግሎትና የኢትዮጵያ ፓትርያርኮች የሠሯቸው ሥራዎችና ያጋጠሟቸው ፈተናዎች ምን እንደነበሩ ይተነትናል፡፡ በምዕራፍ አምስት ኢትዮጵያ ሀገራችን ያሏት ቅርሶች መስፈርቱን አሟልተው በዓለም የቅርስነት የተመዘገቡት የትኞቹ እንደሆኑ፤ ሀገራችንና ቤተ ክርስቲያናችን ከዚህ ዘርፍ ምን ያህል ተጠቃሚ እንደሆኑ የመጽሐፉ አዘጋጅ በአጭሩ አቅርቧል፡፡

አዘጋጁ መጽሐፉ ስለያዛቸው ቁምነገሮች ሲያብራራ

አዘጋጁ መጽሐፉ ስለያዛቸው ቁምነገሮች ሲያብራራ

በመጨረሻም ይህን መጽሐፍ የማዘጋጀት ሀሳቡ የቆየ እንደሆነና የእግዚአብሔር ፈቃድ ታክሎበት ለፍጻሜ በቅቶ በዛሬው ዕለት ለመመረቅ ችሏል፡፡ አግዚአብሔር ቢፈቅድ ብንኖር በቀጣይ ሥራዎቼም እንደምንገናኝ በመጠቆም፤ በዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት አብረውኝ በኤፍራታ መጽሔትና የሰንበት ት/ቤቱን የማስተማሪያ መጻሕፍት በማዘጋጀት ይሠሩ የነበሩት ወንድሞቼና እኅቶቼ ይቺን የመጀመሪያ መጽሐፍ መነሻ አድርገው ከዚህ የተሻለ ሥራ በመሥራት ከሰንበት ት/ቤት ተማሪ የሚጠበቀውን ሓላፊነት በተግባር እንደሚያሳዩ እምነቴ ጽኑ ነው፤ በማለት መጽሐፉን ያዘጋጀበትን ምክንያት አጠቃሏል፡፡
ከአዘጋጁ ምክንያተ ጽሕፈት ገለጻ በኋላ የያዝነው ወር የአብይ ጾም እየተጾመ ያለበት ወቅት በመሆኑን ተጋባዥ በገና ደርዳሪዎች ለታዳሚዎቹ ወቅቱን ያገናዘበ ያሬዳዊ ዝማሬ አቅርበዋል፡፡

በማስከተል ቀሲስ ሰሎሞን ወንድሙ ስለ መጽሐፉ ጠቀሜታ ያዘጋጁትን የዳሰሳ ጥናት (Book Review) ተንትነዋል፡፡ መጽሐፉ 38 አበይትና 40 ንዑሳን ርእሳት የያዘ እንደሆነና ጠንካራ ጎኖችም የሚከተሉት እንደሆኑ ከምልከታቸው በመነሳት አብራርተዋል፡፡

ቀሲስ ሰሎሞን ወንድሙ የዳሰሳ ጥናቱን ሲተነትኑ

ቀሲስ ሰሎሞን ወንድሙ የዳሰሳ ጥናቱን ሲተነትኑ

ጠንካራ ጎኖች

• መጽሐፉ መጠቁም (Index) ስለተዘጋጀለት በቀላሉ የቦታና የሰው ስሞችን መለየት እንደሚያስችልና በአብዛኛውን ጊዜ መጠቁም የማዘጋጃ የአማርኛ ሶፍት ዌር ባለመኖሩ ሥራውን ለመሥራት አስቸጋሪ ያደርገዋል፡፡ አዘጋጁ ግን ይህንን ሁሉ ተቋቁሞ መጠቁም በመሥራቱ የተለየ ያደርገዋል፡፡
• የኢትዮጵያንና የቤተ ክርስቲያንን ታሪክ ለማስረዳት በማስረጃነት የገቡት ፎቶዎች በተገቢው ቦታ መቀመጣቸው አግባብ መሆኑን፤
• የመጽሐፉ የሥነ ጽሑፍ ፍስት መሳጭና የቤተ ክርስቲያንን ቃላትና ሆሄያት በትክክል መጠቀሙ የተለየ ያደርገዋል፡፡
• የግርጌ ማስታወሻ (Foot Note) መኖሩ አንባቢው በቀላሉ ከሌሎች መጻሕፍት ተጨማሪ መረጃ እንዲያገኝ ያግዘዋል፡፡
• የኢትዮጵያንና የቤተ ክርስቲያንን የረጅም ዘመን ታሪክ አካቶ በሚስብ መልኩ መያዙ ጥናትና ምርምር ለሚያደርጉ ወጣት ተመራማሪያን በመረጃነት ያገለግላል፡፡ በማለት የዳሰሳ ጥናት ያቀረቡት ቀሲስ ሰሎሞን የመጽሐፉ ጠንካራ ጎንኑ ያሳየናል ብለዋል፡፡
የመጽሐፉ ክፍተት ናቸው ብለው ያሰቡትን ሲገልጹ፡-

የመጽሐፍ ምረቃ መርሐ ግብሩ አጠቃላይ ገጽታም ይህን ይመስል ነበር፡፡ አጸደ ማርያም ከአራዳ ጊዮርጊስ

ተጨማሪ የግርጌ ማስታወሻ መጽሐፉ ቢኖረው ከያዘው ፍሬ ነገር አኳያ የበረጠ ጥሩ ይሆን ነበር፡፡
• ርቱዕዓ ሃይማኖት ኢትዮጵያዊ ሊቅ የሆነና በ13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ላይ የነበረ መሆኑና እሱ ስለሠራቸው ሥራዎች ቢካተት የመጽሐፉን ጠንካራነት በተሻለ ያጎላው ነበር፡፡
• አልፎ አልፎ የፊደላት ግድፈት ታይተውበታል፤ ይህ ክፍተት በሁሉም መጻሕፍት ላይ የሚከሰት ችግር ቢሆንም አርትኦት ላይ ጥንቃቄ ቢደረግ፤ በቀጣዩ ኅትመት ላይ ተስተካክሎ ቢወጣ፤ ብለው የተዘጋጁበትን የዳሰሳ ጥናት ቋጭተዋል፡፡
በቀረበው ዳሰሳ ላይ ከታዳሚዎቹ አስተያየት ተሰጥቷል፡፡

‹‹እጅግ በርካታ ቁም ነገሮችን የያዘና ለኮሌጃችን ደቀ መዛሙርት በማስተማሪያነት ሊያገለግል ይችላል፡፡ ስለሆነም ወንድማችን ዘሪሁን ይህን የመሰለ ሥራ በመሥራቱ ሊደገፍ ይገባል፤ የሰንበት ት/ቤቶቻችን ልጆች ከዚህ አርአያነት ካለው ተግባር ሊማሩ ይገባቸዋል›› የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ መምህርና የጥናትና ምርምር ሓላፊ መምህር ቸርነት አበበ

‹‹እጅግ በርካታ ቁም ነገሮችን የያዘና ለኮሌጃችን ደቀ መዛሙርት በማስተማሪያነት ሊያገለግል ይችላል፡፡ ስለሆነም ወንድማችን ዘሪሁን ይህን የመሰለ ሥራ በመሥራቱ ሊደገፍ ይገባል፤ የሰንበት ት/ቤቶቻችን ልጆች ከዚህ አርአያነት ካለው ተግባር ሊማሩ ይገባቸዋል››
የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ መምህርና
የጥናትና ምርምር ሓላፊ መምህር ቸርነት
አበበ

‹‹በርቀት ትምህርት ስንማር ያስደስተን የነበረው የዓምደ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት በአባላቱ መጽሐፍ ተዘጋጅቶ ለምረቃ በመጠራቴ ክፍ ያለ ኩራት ተሰምቶኛል፡፡ የመምህራችን የዘሪሁንም መጽሐፍ የያዘው ቁም ነገር በርካታ ነው፤ ሁላችንም ከእሱ ሥራ ተምረን ለቤተ ክርስቲያናችን በተሠማራንበት የሥራ መስክ የተሻለ አስተዋጽኦ በማበርከት እገዛ ብናደርግ ለውጥ እናመጣለን›› የበጸጋህ እናቶችና ሕፃናት ሆስፒታል ባለቤት ዶ/ር ሲሳይ ማሩ

‹በርቀት ትምህርት ስንማር ያስደስተን የነበረው የዓምደ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት በአባላቱ መጽሐፍ ተዘጋጅቶ ለምረቃ በመጠራቴ ክፍ ያለ ኩራት ተሰምቶኛል፡፡ የመምህራችን የዘሪሁንም
መጽሐፍ የያዘው ቁም ነገር በርካታ ነው፤ ሁላችንም ከእሱ ሥራ ተምረን ለቤተ ክርስቲያናችን በተሠማራንበት የሥራ መስክ የተሻለ አስተዋጽኦ በማበርከት እገዛ ብናደርግ ለውጥ እናመጣለን›› የበጸጋህ እናቶችና ሕፃናት ሆስፒታል
ባለቤት ዶ/ር ሲሳይ ማሩ

የጉባኤው አወያይ ወንድማች ተስፋዬ ያለው ለመጽሐፉ አዘጋጅና የዳሰሳ ጥናት አቅራቢው ከታዳሚው ለተለሱላቸው ጥያቄዎችና አስተያየቶች መልስ እንዲሰጡ መድረኩን አመቻችቷል፡፡

የጉባዔው አወያይ ወንድማችን ተስፋዬ ያለው

የጉባዔው አወያይ ወንድማችን ተስፋዬ ያለው

ለቀረቡ አስተያየትና ጥያቄዎች ምላሽ ሲሰጥ

ለቀረቡ አስተያየትና ጥያቄዎች ምላሽ ሲሰጥ

የመጽሐፉ አዘጋጅ ዘሪሁን መንግሥቱ ‹‹ለቀጣይ ሥራዎቼ የሚያግዙ ግብአት ከታዳሚዎቹ በማግኘቴ ምስጋናዬን አቀርባለሁ››፡፡ በማለት ምላሽ ከሰጠበት በኋላ መርሐ ግብሩ በአባ አሥራተ ማርያም ደስታ በጸሎት ተዘግቷል፡፡

የመጽሐፍ ምረቃ መርሐ ግብሩ አጠቃላይ ገጽታም ይህን ይመስል ነበር፡፡ አጸደ ማርያም ከአራዳ ጊዮርጊስ

DSC_0062

 

 

ነጽሮተ ሀገር መጽሐፍ ተመረቀ

ነጽሮተ ሀገር መጽሐፍ ተመረቀ

ነጽሮተ ሀገር መጽሐፍ ተመረቀ

የመጽሐፍ ምረቃ መርሐ ግብሩ አጠቃላይ ገጽታም ይህን ይመስል ነበር፡፡ አጸደ ማርያም ከአራዳ ጊዮርጊስ

የመጽሐፍ ምረቃ መርሐ ግብሩ አጠቃላይ ገጽታም ይህን ይመስል ነበር፡፡
አጸደ ማርያም ከአራዳ ጊዮርጊስ

DSC_0005 DSC_0062

በአጸደ ማርያም

ነጽሮተ ሀገር በሚል ርዕስ በዘሪሁን መንግሥቱ የተዘጋጀው መጽሐፍ በአራዳ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊየርጊስ ቤተ ክርስቲያን ስብከተ ወንጌል አዳራሽ የካቲት 28 ቀን 2007 ዓ.ም.
ተመረቀ፡፡

 

10428540_870432973016746_6517387552534773282_n

መጽሐፉ ስለ ኢትዮጵያ ጥንታዊነት፣ ስለ ቅርሶቿ፣ የቱሪስት መስህብ መሆኗንና የቤተ ክርስቲያንን ሐዋርያዊ ተልእኮ የሚዳስስ በመኾኑ መጠሪያውን ነጽሮተ ሀገር (ሀገር ማየት) መባሉን የአቶ ዘሪሁን ገለጻ ያስረዳል፡፡

DSC_0024

የመጽሐፉ ደራሲ አቶ ዘሪሁን መንግሥቱ መጽሐፉ በውስጡ ስለያዛቸው ቁም ነገሮች ሲገልጽ ‹‹አምስት ምዕራፎች ያሉት ሲሆን፤ በመጀመሪያው ምዕራፍ የኢትዮጵያ የስሟ ትርጓሜ፤ የሀገሪቷ መገለጫዎች፤ በሁለተኛው ምዕራፍ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለሀገሪቱ ያበረከተችው አስተዋጽኦ፤ በሦስተኛው ምዕራፍ የቤተክርስቲያኗን ዓለም አቀፍ ግንኙነት፤ በምዕራፍ አራት ኢትዮጵያ መንበረ ፕትርክና እንዴት እንዳገኘች፣ በዘመኑ የነበሩ ነገሥታት ያበረከቱትን አስተዋጽኦ፤ ከግብጽ ወደ ኢትዮጵያ ተሹመው የመጡ ጳጳሳት አገልግሎትና የኢትዮጵያ ፓትርያርኮች የሠሯቸው ሥራዎችና ያጋጠሟቸው ፈተናዎች ምን እንደነበሩ ይተነትናል፡፡ በምዕራፍ አምስት ኢትዮጵያ ሀገራችን ያሏት ቅርሶች መስፈርቱን አሟልተው በዓለም የቅርስነት የተመዘገቡት የትኞቹ እንደሆኑ፤ ሀገራችንና ቤተ ክርስቲያናችን ከዚህ ዘርፍ ምን ያህል ተጠቃሚ እንደሆነች ያሳያል ብሏል፡

DSC_0057

አግዚአብሔር ቢፈቅድ በቀጣይ ሌሎች ሥራዎችን ይዞ እንደሚቀርብ የገለጽው ደራሲው ‹‹በዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት አብረውኝ በኤፍራታ መጽሔትና የሰንበት ት/ቤቱን የማስተማሪያ መጻሕፍት በማዘጋጀት ይሠሩ የነበሩት ወንድሞቼና እኅቶቼ በዚህ መጽሐፍ መነሻነት ከዚህ የተሻለ ሥራ በመሥራት ከሰንበት ት/ቤት ተማሪ የሚጠበቀውን ሓላፊነት›› በተግባር እንዲያሳዩ አቅርቧል፡፡
የመጽሐፉን የዳሰሳ ጥናት ያካሔዱት ቀሲስ ሰሎሞን ወንድሙ የመጽሐፉ ጠቀሜታ ሲገልጹ፡- መጽሐፉ 38 አበይትና 40 ንዑሳን ርእሳት የያዘ እንደሆነ አብራርተዋል፡፡

የመጽሐፉን ጠንካራ ጎኖች ሲዘረዝሩም፡-

መጽሐፉ መጠቁም (Index) ስለተዘጋጀለት በቀላሉ የቦታና የሰው ስሞችን መለየት እንደሚያስችልና በአብዛኛውን ጊዜ መጠቁም የማዘጋጃ የአማርኛ ሶፍት ዌር ባለመኖሩ ሥራውን ለመሥራት አስቸጋሪ ያደርገዋል፡፡ አዘጋጁ ግን ይህንን ሁሉ ተቋቁሞ መጠቁም በመሥራቱ የተለየ ያደርገዋል፡፡
• የኢትዮጵያንና የቤተ ክርስቲያንን ታሪክ ለማስረዳት በማስረጃነት የገቡት ፎቶዎች በተገቢው ቦታ መቀመጣቸው አግባብ መሆኑን፤
• የመጽሐፉ የሥነ ጽሑፍ ፍስት መሳጭና የቤተ ክርስቲያንን ቃላትና ሆሄያት በትክክል መጠቀሙ የተለየ ያደርገዋል፡፡
• የግርጌ ማስታወሻ (Foot Note) መኖሩ አንባቢው በቀላሉ ከሌሎች መጻሕፍት ተጨማሪ መረጃ እንዲያገኝ ያግዘዋል፡፡

• የኢትዮጵያንና የቤተ ክርስቲያንን የረጅም ዘመን ታሪክ አካቶ በሚስብ መልኩ መያዙ ጥናትና ምርምር ለሚያደርጉ ወጣት ተመራማሪያን በመረጃነት ያገለግላል፡፡

ጥናት አቅራቢው የመጽሐፉ ክፍተት ያሏቸውን ሲገልጹ፡-

DSC_0035

ከያዘው ፍሬ ነገር አኳያ ተጨማሪ የግርጌ ማስታወሻ መጽሐፉ ቢኖረው የበለጠ ይሆን ነበር፡፡
• ኢትዮጵያዊ ሊቅ ርቱዕዓ ሃይማኖት በ13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ላይ የነበረ መሆኑ ቢጠቀስ በተሻለ ያጎላው ነበር፡፡
• አልፎ አልፎ የፊደላት ግድፈት ታይተውበታል፤ ይህ ክፍተት በሁሉም መጻሕፍት ላይ የሚከሰት ችግር ቢሆንም አርትኦት ላይ ጥንቃቄ ቢደረግ፤ በቀጣዩ ኅትመት
ላይ ተስተካክሎ ቢወጣ፤ ብለው የዳሰሳ ጥናታቸውን ቋጭተዋል፡

የታዳሚዎቹ አስተያየት

‹‹እጅግ በርካታ ቁም ነገሮችን የያዘና ለኮሌጃችን ደቀ መዛሙርት በማስተማሪያነት ሊያገለግል ይችላል፡፡ ስለሆነም ወንድማችን ዘሪሁን ይህን የመሰለ ሥራ በመሥራቱ ሊደገፍ ይገባል፤ የሰንበት ት/ቤቶቻችን ልጆች ከዚህ አርአያነት ካለው ተግባር ሊማሩ ይገባቸዋል›› የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ መምህርና የጥናትና ምርምር ሓላፊ መምህር ቸርነት አበበ

‹‹እጅግ በርካታ ቁም ነገሮችን የያዘና ለኮሌጃችን ደቀ መዛሙርት በማስተማሪያነት ሊያገለግል ይችላል፡፡ ስለሆነም ወንድማችን ዘሪሁን ይህን የመሰለ ሥራ በመሥራቱ ሊደገፍ ይገባል፤ የሰንበት ት/ቤቶቻችን ልጆች ከዚህ አርአያነት ካለው ተግባር ሊማሩ ይገባቸዋል››
የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ መምህርና
የጥናትና ምርምር ሓላፊ መምህር ቸርነት
አበበ

‹‹በርቀት ትምህርት ስንማር ያስደስተን የነበረው የዓምደ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት በአባላቱ መጽሐፍ ተዘጋጅቶ ለምረቃ በመጠራቴ ክፍ ያለ ኩራት ተሰምቶኛል፡፡ የመምህራችን የዘሪሁንም መጽሐፍ የያዘው ቁም ነገር በርካታ ነው፤ ሁላችንም ከእሱ ሥራ ተምረን ለቤተ ክርስቲያናችን በተሠማራንበት የሥራ መስክ የተሻለ አስተዋጽኦ በማበርከት እገዛ ብናደርግ ለውጥ እናመጣለን›› የበጸጋህ እናቶችና ሕፃናት ሆስፒታል ባለቤት ዶ/ር ሲሳይ ማሩ

‹‹በርቀት ትምህርት ስንማር ያስደስተን የነበረው የዓምደ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት በአባላቱ መጽሐፍ ተዘጋጅቶ ለምረቃ በመጠራቴ ክፍ ያለ ኩራት ተሰምቶኛል፡፡ የመምህራችን የዘሪሁንም
መጽሐፍ የያዘው ቁም ነገር በርካታ ነው፤ ሁላችንም ከእሱ ሥራ ተምረን ለቤተ ክርስቲያናችን በተሠማራንበት የሥራ መስክ የተሻለ አስተዋጽኦ በማበርከት እገዛ ብናደርግ ለውጥ እናመጣለን›› የበጸጋህ እናቶችና ሕፃናት ሆስፒታል
ባለቤት ዶ/ር ሲሳይ ማሩ

የመጽሐፍ ምረቃ መርሐ ግብሩ አጠቃላይ ገጽታም ይህን ይመስል ነበር፡፡ አጸደ ማርያም ከአራዳ ጊዮርጊስ

የመጽሐፍ ምረቃ መርሐ ግብሩ አጠቃላይ ገጽታም ይህን ይመስል ነበር፡፡
አጸደ ማርያም ከአራዳ ጊዮርጊስ

የመጽሐፍ ምረቃ መርሐ ግብሩ አጠቃላይ ገጽታም ይህን ይመስል ነበር፡፡ አጸደ ማርያም ከአራዳ ጊዮርጊስ

የመጽሐፍ ምረቃ መርሐ ግብሩ አጠቃላይ ገጽታም ይህን ይመስል ነበር፡፡
አጸደ ማርያም ከአራዳ ጊዮርጊስ